Register  
Wednesday, February 22, 2012
Home » Communication » ERA News » Amharic Version  

  • ERA Bridges
  • ERA at Road Construction
  • Bridges
  • Addis - Adama Supper Highway

ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የኢመባ ማኔጅመንትና ሠራተኞች 20.5 ሚሊዮን ብር አዋጡ::

Minimize

 በቅርቡ በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን በይፋ የመሰረት ድንጋይ የተጣለለትንና በትልቅነቱና በኃይል ማመንጨት አቅሙ በዓለም ደረጃ አሥረኛ እንዲሁም በአፍሪካ ደረጃ አንደኛ ይሆናል ተብሎ የሚጠበቀውን የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ለመደገፍ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን ማኔጅመንትና ሠራተኞች ከወር ደመወዛቸው 20.5 ሚሊዮን ብር አዋጡ ::

የዩኒቨርሳል የገጠር መንገድ ተደራሽነት ፕሮግራም(URRAP)ን ለማሳካት የሚያስችል የሰው ኃይል ልማት የመጀመሪያ ዙር ስልጠና ምረቃ ተካሄደ ::

Minimize

በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት አገሪቱን ወደላቀ የእድገት ደረጃ ለማድረስ በመንግስት የተነደፈውን ሁሉንም የአገሪቱን ቀበሌዎች በመንገድ የማገናኘት ፕሮግራም(URRAP) በስኬታማ ሁኔታ ለማሳካት የሚያስችል የሰው ኃይል ልማት የመጀመሪያ ዙር ስልጠና ምረቃ ሥነ-ሥርዓት መጋቢት 30 ቀን 2003 ዓ.ም በጫንጮ/ጊንጪ በሚገኘው የባለሥልኑ ማሰልጠኛ  ማዕከል መካሄዱን የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን አስታወቀ::

የአምስት ዓመቱን የመንገድ ልማት እቅድ ለማሳካት የሚያስችል የሙያ ብቃት መመዘኛ የምክክር መድረክ ተካሄደ ::

Minimize

በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት አገሪቱን ወደላቀ የእድገት ደረጃ ለማድረስ በመንግስት የተነደፈውን የመንገድ ዘርፉን የእድገትና የትራንስፎርሜሽን እቅድ በስኬታማ ሁኔታ ለማሳካት የሚያስችል የሙያ ብቃት መመዘኛ የምክክር መድረክ መጋቢት 15 ቀን 2003 ዓ.ም በዓለም ገና በሚገኘው የባለሥልኑ የስብሰባ አደራሽ መካሄዱን የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን አስታወቀ::

የጋምቤላ-ኢታንግ -ጂካዎ የመንገድ ግንባታ በአብዛኛው የአፈር ሙሌት ሥራ ተጠናቆ የአስፋልት ማንጠፍ ሥራ ተጀመረ ::

Minimize

በጋምቤላ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የሚገኘውና በኢመባ ኦፕሬሽን በሠራት ላይ ያለው የጋምቤላ-ኢታንግ-ጂካዎ የመንገድ ግንባታ በአብዛኛው የአፈር ሙሌት ሥራ ተጠናቆ የአስፋልት ማንጠፍ ሥራ መጀመሩን የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥጣን አስታወቀ::

መጋቢት 20 2003 ዓ.ም ከ 3.3 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የአምስት መንገዶች የኮንትራት ስምምነቶች ተፈረሙ ፡፡

Minimize

የኢትዮጵያ መንግስት የቀረፀዉ የአራተኛዉ የመንገድ ዘርፍ ልማት ፕሮግራም አካል የሆኑት የመቀሌ አብአዲ-አድዋ መስመር የኮንትራት አንድ እና የኮንትራት ሁለት የመሀሌ-ስረት መንደር ፤የስረት መንደር ወረይ እንዲሁም የደባርቅ-ቡሃይት እና የቡሃይት-ድልይብዛ የመንገድ ፕሮጀክቶችን ደረጃ ለማሳደግና የሞምባሳ-ናይሮቢ-አዲስ አበባ ኮሪደር የሆነዉ አገረማርያም-ሜጋ መንገድ ማጠናከር ፕሮጀክት ኮንትራት አንድ አገረማርያም-ያቤሎ መንገድ በአስፋልት ኮንክሪት ፔቭመንት ደረጃ ለማጣናከር የሚያስችሉ የዉል ስምምነቶች ዛሬ መጋቢት 20 ቀን 2003 ዓ.ም. በባለስልጣኑ የመሰብሰብያ አዳራሽ ተፈረሙ ፡፡   

 

Minimize
የመንገድ ዘርፍ አሰራርን ለማሻሻል እና የግንባታ ዋጋ ንረትን ለመቆጣጠር የሚያስችሉ ስትራቴጅዎች ተነድፈዉ በትግበራ ሂደት ላይ ይገኛሉ ፡፡
የመንገድ ዘርፉን አሰራርን ለማሻሻል የዋጋ ንረትን ለመቆጣጠር የአምስት አመት እቅድ ወጥቶ እንቅስቃሴ ተጀምሯል ፡፡ በዚህ ረገድም 16 ፕሮጀክቶች ተቀርፀዉ ከሐምሌ 2002 ጀምሮ በተቀናጀ መልኩ እየተከናወኑ ይገኛሉ ፡፡  Read More ………………..

 

ከሻሸመኔ - ዶዶላ የሚወሰደዉ 70 ኪ.ሜ. ሜትር መንገድ ተመረቀ

Minimize
  የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን በሶስተኛዉ የመንገድ ልማት ዘርፍ ፕሮግራም ከሚያስገነባቸዉና ከሚያሻሽላቸዉ መንገዶች ዉስጥ አንዱ አካል የሆነዉ በኦሮሚያ ብ/ክ/መንግስት የሚገኘዉ ሻሸመኔ - ኪ.ሜ. 35 እና ኪ.ሜ. 35 - ዶዶላ መገንጠያ በአጠቃላይ 70 ኪ.ሜ. አስፋልት ኮንክሪት መንገድ የግንባታ ሥራዉ ተጠናቅቆ መስከረም 21 ቀን 2003 ዓ.ም. ተመረቀ ፡፡

 

 

Minimize

ከ 179.9 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባዉ የሳዉላ - ቃቆ (ኮንትራት 1) መንገድ ተመረቀ

    የኢፌዴሪ መንግስት በሶስተኛዉ የመንገድ ዘርፍ ልማት ፕሮግራም ከሚያስገነባቸዉና ከሚያሻሽላቸዉ መንገዶች ዉስጥ አንዱ የሆነዉ እና በደቡብ ብ/ብ/ሕ/ክ/መንግስት የሚገኘዉ የሳዉላ - ቃቆ (ኮንትራት 1) ፕሮጀክት ደረጃዉን በጠበቀ የጠጠር መንገድ የግንባታ ሥራዉ ተጠናቆቅ ጥቅምት 14 ቀን 2003 ዓ.ም. ተመርቋል ፡፡

ግንባታዉ አገር በቀል የሥራ ተቋራጭ በሆነዉ በአኪር ኮንስትራክሽን የተከናወነዉ ይህዉ መንገድ ከ179.9 ሚሊዮን ብር በላይ የፈጀ ሲሆን፤ አጠቃላይ ወጪዉም በኢትዮጵያ መንግስት ተሸፍኗል፡፡ የፕሮጀክቱን የምህነድስና ቁጥጥርና የማማከር ስራ መታፈሪያ ኮንሰልቲንግ ኃ/የተ/የግ/ኩ የተባለ አገር በቀል ድርጅት አከናዉኖታል ፡፡                                                                                              
                                           Read more here ........... 
Copyright 2011 - Ethiopian Roads Authority   |  Privacy Statement  |  Terms Of Use