Skip to Content
Amharic English

NEWS NEWS

የአዲስ - ጊቤ ከባድ ጥገና ፕሮጀክት በተሻለ እንቅስቃሴ ላይ ይገኛል

  አዲስ አበባ፣ መጋቢት 16፣ 2017 (ኢ መ አ):- የአዲስ አበባ - ጅማ ዋና መንገድ አካል የኾነው የአዲስ-ጊቤ አስፋልት መንገድ ከባድ ጥገና ፕሮጀክት በተሻለ እንቅስቃሴ ላይ ይገኛል። መንገዱ ከፍተኛ የትራፊክ ፍሰት የሚያስተናግድ በመሆኑና በአገልግሎት ብዛት በመጎዳቱ ምክንያት ነው ከባድ ጥገና እየተደረገለት የሚገኘው። ከዚህም ባሻገር የወጪ ንግድም መተላለፊያ በመኾኑ የመስመሩን ከፍተኛ የትራፊክ ፍሰት በሚመጥን መልኩ መልሶ ግንባታ እየተደረገለት ነው። የከባድ ጥገና ፕሮጀክቱ ለግንባታ አመቺነት ሲባል በሁለት ክፍሎች ተከፋፍሎ እየተከናወነ ይገኛል። ለጥገናው በድምሩ 3 ቢሊዮን ብር የተመደበ ሲኾን፥ ሙሉ ወጪው በፌደራል መንግስት ይሸፈናል። በክፍል - 2 የአዲስ -ጊቤ ወንዝ የመልሶ ግንባታ ፕሮጀክት 64 ኪሎሜትር የሚሸፍን ኾኖ፥ መነሻውን... Read More About የአዲስ - ጊቤ ከባድ ጥገና ፕሮጀክት በተሻለ እንቅስቃሴ ላይ ይገኛል »

የሀሚድ ድልድይ ለትራፊክ አገልግሎት ክፍት ተደረገ

  አዲስ አበባ፣ መጋቢት 13፣ 2017 (ኢ መ አ):- የወልዲያ - ሮቢት መንገድ ክፍል የኾነው የሀሚድ ወንዝ የብረት ድልድይ ጥገናው መጠናቀቁን ተከትሎ ለትራፊክ አገልግሎት ክፍት ተደርጓል። ድልድዩ ከዚህ ቀደም ከተፈቀደው ክብደት በላይ በጫነ ከባድ ተሽከርካሪ ጉዳት ደርሶበት እንደነበር ይታወቃል። በወቅቱ ተለዋጭ መንገድ በማዘጋጀት ተሽከርካሪዎች እንዲገለገሉ ማድረግ ተችሏል። የብረት ድልድዩን መልሶ ለመገንባትም በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የኮምቦልቻ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት እንዲሁም የድልድይ እና ስትራክቸር ዳይሬክቶሬት ባደረጉት ከፍተኛ ርብርብ ድልድዩን በአጭር ጊዜ ውስጥ በመጠገን ለትራንስፖርት እንቅስቃሴ ክፍት ማድረግ ተችሏል። 45 ነጥብ 7 ሜትር ርዝመት ያለው ይኸው ድልድዩ አሁን ላይ ሙሉ በሙሉ ክፍት ተደርጎ አገልግሎት እየሰጠ... Read More About የሀሚድ ድልድይ ለትራፊክ አገልግሎት ክፍት ተደረገ »

የባቱ - አርሲነገሌ የፍጥነት መንገድ ግንባታ 84 ነጥብ 50 በመቶ ደረሰ

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 10፣ 2017 (ኢ መ አ):- የአዲስ አበባ-ሞያሌ-ናይሮቢ-ሞምባሳ የመንገድ ኮሪደር አካል የሆነው የሞጆ-ሐዋሳ ኮንትራት 3 ፡ ባቱ - አርሲነገሌ የፍጥነት መንገድ ግንባታ 84 ነጥብ 50 በመቶ ደርሷል፡፡ 57 ኪሎ ሜትር በሚረዝመው የመንገዱ ግንባታ የእስካሁን ሂደትም የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት ፣ የውሃ መፋሰሻ ቦዮች (Side Ditches) ፣ የሰብ ቤዝ እና ቤዝ ኮርስ ፣ ሚዛን ጣቢያዎች እና ዞሮ መመለሻ መንገዶች ፣ የስትራክቸር ፣ የመኪና መሸጋገሪያ ፣ የእግረኛ/የእንስሳት መሸጋገሪያ ፣ የወንዝ ድልድዮች ፣ የመንገድ ዳር አጥር ፖሎች የማምረት ፣ የ Intelligent Transport System (ITS) ቱቦ ቀበራ ፣ የአስፋልት ማንጠፍ እንዲሁም በዋናው መንገድ እና አገናኝ መንገዶች ላይ ሌሎች የተለያዩ ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ። ... Read More About የባቱ - አርሲነገሌ የፍጥነት መንገድ ግንባታ 84 ነጥብ 50 በመቶ ደረሰ »

የሙስሊ - ኮሪ - ቴሩ ምዕራፍ አንድ የመንገድ ፕሮጀክት የአስፋልት ንጣፍ እየተከናወነለት ነው

  ሰመራ፣ መጋቢት 10፣ 2017 (ኢ መ አ):- በአፋር ክልል የሙስሊ - ኮሪ - ቴሩ መንገድ ፕሮጀክት የመጀመሪያው ምዕራፍ ከኪሎሜትር 00 እስከ ኪሎሜትር 84 ያለው የአስፋልት ንጣፍ እየተከናወነለት ነው። የመንገድ ግንባታው 84 ነጥብ 2 ኪሎሜትር የሚሸፍን ሲኾን፥ በአፋር ክልል አውሲረሱ እና ፋንቲረሱ ዞኖች ውስጥ የሚገኙ ሁለት ወረዳዎችን እና በርካታ ቀበሌዎችን ያስተሳስራል። አሁን ላይ የ20 በመቶ የውኃ መፋሰሻ ቱቦ፣ የ21 በመቶ የስትራክቸር፣ የ98 በመቶ የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት፣ የ34 በመቶ ሰብቤዝ እንዲሁም የ10 በመቶ የአስፋልት ንጣፍ ሥራዎች ተከናውነዋል። የሰባት ድልድዮች ግንባታም በፕሮጀክቱ ተካትቷል። በአሁኑ ወቅት የፕሮጀክቱ አጠቃላይ አፈጻጸም 56 በመቶ ደርሷል። የተመዘገበውን አበረታች አፈጻጸም አጠናክሮ ለማስቀጠል በትኩረት... Read More About የሙስሊ - ኮሪ - ቴሩ ምዕራፍ አንድ የመንገድ ፕሮጀክት የአስፋልት ንጣፍ እየተከናወነለት ነው »

የመንገድ ዘርፍ አፈጻጸም ላይ የሚታዩ ተግዳሮቶች እና ቀጣይ አካሄዶች ላይ ውይይት ተካሄደ

  የከተማ እና መሠረተ ልማት ሚንስትር ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ የኢ መ አ መንገድ ምርምር ማዕከልን ጎብኝተዋል አዲስአበባ፣ መጋቢት 09፣ 2017 (ኢ መ አ):- የመንገድ ዘርፍ አፈጻጸም ላይ የሚታዩ ተግዳሮቶች እና ቀጣይ አካሄዶች ላይ በኢ መ አ የመንገድ ምርምር ማዕከል ውይይት ተካሂዷል። በውይይቱ ላይ በመንገድ ዘርፍ ባለፉት ዓመታት የተመዘገቡ ስኬቶች፣ ዘርፉን የገጠሙት ተግዳሮቶች እና ቀጣይ የመፍትሄ አቅጣጫዎች ላይ ገለጻ ተደርጓል። በተጨማሪም ከሚንስቴር መ/ቤቱ ድጋፍ ሊደረግባቸው የሚችሉ ጉዳዮችም ተለይተው ቀርበዋል።  በዚህም ረገድ የሀገሪቷን የመንገድ ሽፍን የመንገድ ዘርፍ ልማት ፕሮግራሙ በ1989 ከነበረበት 23 ሺህ ኪሎሜትር አሁን ላይ ወደ 171 ሺህ ማድረስ እንደተቻለ ገላጻው ላይ ተጠቁሟል። ሆኖም ባለፉት ጊዜያት የጋጠሙ... Read More About የመንገድ ዘርፍ አፈጻጸም ላይ የሚታዩ ተግዳሮቶች እና ቀጣይ አካሄዶች ላይ ውይይት ተካሄደ »

ERA GIS PORTAL ERA GIS PORTAL

20TH REGIONAL CONFERNCE 20TH REGIONAL CONFERNCE

URGENT NOTICE URGENT NOTICE

CALL FOR Workshop CALL FOR Workshop

FINANCIAL TRANSPARENCY & ACOUNTABLITY FINANCIAL TRANSPARENCY & ACOUNTABLITY

— 5 Items per Page
Showing 1 - 5 of 6 results.

FIND US ON GOOGLE MAP FIND US ON GOOGLE MAP